Advertorials | Aug 13,2026
Jan 17 , 2026
የዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (አይ ኤም ኤፍ) ለኢትዮጵያ የ48 ወራት የብድር ፕሮግራም አፈጻጸም አራተኛውን ዙር ግምገማ ካጠናቀቀ በኋላ የ261 ሚሊዮን ዶላር ክፍያ እንዲለቀቅ ወሰነ። ባለፈው ሐሙስ በዋሽንግተን ዲሲ የተሰበሰበው የድርጅቱ የሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ያሳለፈው ይህ ውሳኔ እ.ኤ.አ. በ2024 አጋማሽ የጸደቀውን የ3.4 ቢሊዮን ዶላር አጠቃላይ ድጋፍ ተከትሎ እስካሁን የተለቀቀውን የገንዘብ መጠን 2.18 ቢሊዮን ዶላር አድርሶታል። ይህ በሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ አገራት ድርጅቱ ከሚሰጠው የገንዘብ ድርሻ አንጻር ከፍተኛው የድጋፍ መጠን ነው።
አይ ኤም ኤፍ በቅርብ ግምገማው የኢትዮጵያን የማክሮ ኢኮኖሚ አፈጻጸም “ከሚጠበቀው በላይ” ሲል አወድሶታል። ድርጅቱ ለዚህ በማሳያነት የጠቀሰው መሻሻል የታየበትን የሀገር ውስጥ ምርት ዕድገት፣ የኤክስፖርት ገቢ መጨመርን፣ የተሻሻለ የሀገር ውስጥ ገቢ አሰባሰብን፣ የውጭ ምንዛሬ ክምችት ማደግን እና የዋጋ ግሽበት መቀዝቀዝን ነው። ዓርብ ጥር 8 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው ይፋዊ መግለጫ አይ ኤም ኤፍ "ሁሉም የአፈጻጸም መስፈርቶች የተሟሉ ሲሆን አብዛኞቹ አመላካች ግቦችም ተሳክተዋል" ብሏል።
ይሁን እንጂ የቦርዱ ይሁንታ በጥንቃቄ የታጀበ ነበር። የአይ ኤም ኤፍ ምክትል ማኔጂንግ ዳይሬክተር ናይጄል ክላርክ በምንዛሬና በገንዘብ ፖሊሲው ላይ የታዩ ለውጦችን ቢያደንቁም በ2018 ዓ.ም. የፌዴራል በጀት ላይ የታዩ መዛባቶች ቀደም ሲል ከተስማሙት የፋይናንስ ማዕቀፎች ውጪ መሆናቸውን ጠቁመዋል። መንግሥት ይህንን የበጀት መዛባት ለማስተካከልና የፋይናንስ ዲስፕሊን ለመጠበቅ ቃል የገባ ሲሆን በብሩክ ታየ (ዶ/ር) የሚመራው የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ኦዲት የተደረገ የፋይናንስ መግለጫ አለመታተሙም ሌላኛው እንደ ክፍተት የተጠቀሰ ጉዳይ ነው።
በአዲሱ ስምምነት መሠረት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በውጭ ምንዛሬ ገበያ ላይ የሚያደርገውን ጣልቃ ገብነት የሚገድብ አዲስ ገደብ ተቀምጧል። ይህም ባንኩ የውጭ ምንዛሬ እንቅስቃሴውን በይፋ ጨረታ ብቻ እንዲያከናውን የሚያስገድድ ሲሆን ዓላማውም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስተዳደር ላይ የሚሰነዘሩ የግልጽነት ጥያቄዎችን ለመመለስና በውጭ ምንዛሬ ገበያው ላይ እምነትን ለመገንባት ነው።
በተጨማሪም አይ ኤም ኤፍ የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲ እንዲቀጥል እና የነዳጅ ድጎማ ደረጃ በደረጃ እንዲነሳ በድጋሚ አሳስቧል።
የኢትዮጵያ የዕዳ ሸክም አሁንም በፕሮግራሙ ላይ ጥላውን ያሳረፈ ሲሆን ከሁለትዮሽ አበዳሪዎች ጋር የመግባቢያ ሰነድ ቢፈረምም ከግል አበዳሪዎች ጋር ያለው ድርድር እስካሁን ባለመቋጨቱ ድርጅቱ ስጋቱን ገልጿል። እ.ኤ.አ. በ2023 የአንድ ቢሊዮን ዶላር ዩሮ ቦንድ ክፍያ ባለመፈጸሟ በይፋ "ዲፎልት" ውስጥ የገባችው ኢትዮጵያ ሹሞቿ ውስብስብ የዕዳ ሽግሽግ ድርድሮችን በማድረግ ላይ ይገኛሉ። መንግሥት ከኮይሻ የኤሌክትሪክ ኃይል ፕሮጀክት ውጭ አዳዲስ የንግድ ብድሮችን ከመውሰድ እንዲቆጠብም ድርጅቱ አሳስቧል።
Photo Gallery | 193402 Views | May 06,2019
Photo Gallery | 183291 Views | Apr 26,2019
Photo Gallery | 180104 Views | Oct 06,2021
My Opinion | 145528 Views | Aug 14,2021
Aug 14 , 2026
Aschalew Fetene, known as “Ardi” and admired for his poetic depth, has built a ti...
Aug 8 , 2026
The World Bank asks readers to picture a mother in rural Ethiopia who has never held...
Jul 31 , 2026
Weldu Yiheysh has not read the Pacific temperature charts. He does not need to. In Shibta District of Enderta Wereda, in...
Jul 25 , 2026
Ideally, citizens who have paid income tax all year should not have to reach for thei...