Photo Gallery | 189643 Views | May 06,2019
Feb 4 , 2026.
ጸደይ ባንክ የምጣኔ ሀብት ባለሙያና የቀድሞውን የብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥ ዮሐንስ አያሌውን (ዶ/ር) በፕሬዝዳንትነት ለመሰየም ተዘጋጅቷል።
በአማራ ክልል ከነበረው የብድርና ቁጠባ ተቋምነት ወደ ባንክ ካደገ በኋላ ሁለተኛው ፕሬዝዳንት ሊሆን የሚችለውን ዕጩ ለይቷል። ይህ የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ውሳኔ ባንኩ በባለፈው ሒሳብ ዓመት የ2.13 ቢሊዮን ብር ኪሳራ ባጋጠመው ወሳኝ ወቅት ላይ የቀረበ ነው።
ዮሐንስ በብሔራዊ ባንክ ተቀባይነት ካገኙ ባለፈው ጥር ወር ላይ ስልጣን የለቀቁትን የጸዳይ ባንክ መስራች ፕሬዝዳንት መኮንን የለውምወሰንን የሚተኩ ሲሆን፤ ካለፈው ጥር ወር ጀምሮ የሺእመቤት ተፈራ ባንኩን በጊዜያዊነት በመምራት ላይ ይገኛሉ።
ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ የሥራ ልምድ ያላቸው ዮሐንስ፣ የቀድሞ የሙያ ዘመናቸው ለዘጠኝ ዓመታት በብሔራዊ ባንክ ዋና የምጣኔ ሀብት ባለሙያነት የተቃኘ ነበር። በፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት እንዲሁም በአፍሪካ ንግድና ኢንቨስትመንት ልማት ኢንሹራንስ የሀገር ውስጥ ዳይሬክተር በመሆንም አገልግለዋል። በተለይም እ.ጎ.አ ከ2018 እስከ 2022 ዓ.ም. በኢትዮጵያ ልማት ባንክ በቆዩባቸው ዓመታት ተቋሙን ከተከማቸ የማይመለስ ብድር በማላቀቅ ወደ ንግድ ተኮር የብድር አሰጣጥ ለማሸጋገር ያደረጉት ጥረት ውጤት የታየበት እንደነበር ይታወሳል። ዮሐንስ በቅርቡ የአማራ ባንክ ፕሬዝዳንት ሆነው በሰሩባቸው 16 ወራት ባንኩ በገንዘብ እጥረትና በውስጥ ቀውስ ውስጥ በነበረበት ወቅት ተረክበውት፣ ከኪሳራ በማውጣት 655 ሚሊዮን ብር ከታክስ በፊት ትርፍ እንዲያስመዘግብና የ85 በመቶ ዕድገት እንዲያሳይ ማስቻላቸው ይታወሳል።
PUBLISHED ON
Feb 04,2026 [ VOL
26 , NO
1345]
Photo Gallery | 189643 Views | May 06,2019
Photo Gallery | 179355 Views | Apr 26,2019
Photo Gallery | 175972 Views | Oct 06,2021
My Opinion | 141685 Views | Aug 14,2021
Jun 13 , 2026
The recent policy decision to fully open freight forwarding to foreign capital may be...
Jun 6 , 2026
For a political veteran as controversial as Getachew Reda, last week's national elect...
May 30 , 2026
Tomorrow, millions of Ethiopians are expected to vote in the seventh national electio...
May 23 , 2026
An International Monetary Fund (IMF) team has spent weeks in Addis Abeba conducting t...