Photo Gallery | 192822 Views | May 06,2019
Dec 30 , 2025.
በኢትዮጵያ ልማት ባንክ ከፍተኛ የሥራ አመራር እርከን ላይ ረጅም ዓመታትን ያስቆጠሩት ጌታቸው ዋቄ ከታኅሣሥ 17 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ከባንኩ ምክትል ፕሬዝዳንትነት ኃላፊነታቸው ተሰናብተዋል። የጌታቸው መሰናበት በባንኩ ውስጥ እየተካሄደ ያለው ሰፊ የአመራር ለውጥ አካል ሲሆን፣ በቅርብ ሣምንታት ካስተናገዳቸው ከፍተኛ የአመራር ሽግሽጎች መካከል አንዱ ሆኗል።
ጌታቸው ከባንኩ የተሰናበቱት ከሁለት አስርተ ዓመታት በላይ በተለያዩ ስትራቴጂካዊ የኃላፊነት ቦታዎች ላይ ካገለገሉ በኋላ ነው። የእሳቸው ስንብት የመጣው፣ ባለፉት ሦስት ሳምንታት ውስጥ ብቻ በባንኩ የሥራ አስፈጻሚዎችና በዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ላይ እየተደረገ ካለው ተከታታይ ለውጥ ጋር ተገጣጥሞ ነው።
ቀደም ሲል ተክለወልድ አጥናፉን በመተካት፣ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ብሩክ ታየ (ዶ/ር) የልማት ባንክ የቦርድ ሰብሳቢ ሆነው መሾማቸው ይታወሳል። ተክለወልድ ለረዥም ዔመታት የብሔራዊ ባንክ ገዢ ሆነው ሰርተዋል::
የብሩክ ሹመት በባንኩ ከፍተኛ አመራሮች ሹመትና መዋቅራዊ የሥልጣን ወሰን ላይ ካሉ ውጥረቶች ጋር ተያይዞ፣ ተቋሙ አዲስ የአመራር አቅጣጫ እንዲይዝ የሚያደርግ ሊሆን ይችላል።
በዚሁ የአመራር ለውጥ ሂደት፣ ኢሳያስ ካሳ (ዶ/ር) እመቤት መለሰን (ዶ/ር) በመተካት የልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ሆነው ተሹመዋል። ኢሳያስ ቀደም ሲል በብሩክ መሪነት በኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ውስጥ ያገለገሉ ሲሆን፣ የሳቸው ወደ ልማት ባንክ መምጣት ተቋሙ በሥራ አስፈፃሚ አባላት ላይ ለውጥ ሊያደርግ እንደሚችል ማሳያ ተደርጎ ተወስዷል።
የባንኩ የቦርድ ሰብሳቢ ብሩክ በሰጡት መግለጫ፣ ጌታቸው ለባንኩ ላበረከቱት የረጅም ዘመን አገልግሎት ምስጋናቸውን አቅርበው ከምክትል ፕሬዝዳንትነት ኃላፊነታቸው መሰናበታቸውን አረጋግጠዋል።
PUBLISHED ON
Dec 30,2025 [ VOL
26 , NO
1340]
Photo Gallery | 192822 Views | May 06,2019
Photo Gallery | 182725 Views | Apr 26,2019
Photo Gallery | 179485 Views | Oct 06,2021
My Opinion | 144968 Views | Aug 14,2021
Aug 8 , 2026
The World Bank asks readers to picture a mother in rural Ethiopia who has never held...
Jul 31 , 2026
Weldu Yiheysh has not read the Pacific temperature charts. He does not need to. In Shibta District of Enderta Wereda, in...
Jul 25 , 2026
Ideally, citizens who have paid income tax all year should not have to reach for thei...
Jul 18 , 2026
Pressed in Parliament on jobs and household incomes, Prime Minister Abiy Ahmed (PhD)...