FORTUNE+ VIDEO SPONSORED CONTENTS ADVERTORIALS FORTUNE AUDIO Fortune Careers TRADE AFRICA Election 2026 New TIME REMAINING UNTIL ETHIOPIA’S NATIONAL ELECTION 0Days 0Hours 0Minutes 0Seconds


በልማት ባንክ ለረጅም ጊዜ ያገለገሉት ምክትል ፕሬዝዳንት ከኃላፊነታቸው ተሰናበቱ

Dec 30 , 2025.


በኢትዮጵያ ልማት ባንክ ከፍተኛ የሥራ አመራር እርከን ላይ ረጅም ዓመታትን ያስቆጠሩት ጌታቸው ዋቄ ከታኅሣሥ 17 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ከባንኩ ምክትል ፕሬዝዳንትነት ኃላፊነታቸው ተሰናብተዋል። የጌታቸው መሰናበት በባንኩ ውስጥ እየተካሄደ ያለው ሰፊ የአመራር ለውጥ አካል ሲሆን፣ በቅርብ ሣምንታት ካስተናገዳቸው ከፍተኛ የአመራር ሽግሽጎች መካከል አንዱ ሆኗል።

ጌታቸው ከባንኩ የተሰናበቱት ከሁለት አስርተ ዓመታት በላይ በተለያዩ ስትራቴጂካዊ የኃላፊነት ቦታዎች ላይ ካገለገሉ በኋላ ነው። የእሳቸው ስንብት የመጣው፣ ባለፉት ሦስት ሳምንታት ውስጥ ብቻ በባንኩ የሥራ አስፈጻሚዎችና በዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ላይ እየተደረገ ካለው ተከታታይ ለውጥ ጋር ተገጣጥሞ ነው።

​ቀደም ሲል ተክለወልድ አጥናፉን በመተካት፣ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ብሩክ ታየ (ዶ/ር) የልማት ባንክ የቦርድ ሰብሳቢ ሆነው መሾማቸው ይታወሳል። ተክለወልድ ለረዥም ዔመታት የብሔራዊ ባንክ ገዢ ሆነው ሰርተዋል::

የብሩክ ሹመት በባንኩ ከፍተኛ አመራሮች ሹመትና መዋቅራዊ የሥልጣን ወሰን ላይ ካሉ ውጥረቶች ጋር ተያይዞ፣ ተቋሙ አዲስ የአመራር አቅጣጫ እንዲይዝ የሚያደርግ ሊሆን ይችላል።

​በዚሁ የአመራር ለውጥ ሂደት፣ ኢሳያስ ካሳ (ዶ/ር) እመቤት መለሰን (ዶ/ር) በመተካት የልማት ባንክ ፕሬዝዳንት ሆነው ተሹመዋል። ኢሳያስ ቀደም ሲል በብሩክ መሪነት በኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ውስጥ ያገለገሉ ሲሆን፣ የሳቸው ወደ ልማት ባንክ መምጣት ተቋሙ በሥራ አስፈፃሚ አባላት ላይ ለውጥ ሊያደርግ እንደሚችል ማሳያ ተደርጎ ተወስዷል።

​የባንኩ የቦርድ ሰብሳቢ ብሩክ በሰጡት መግለጫ፣ ጌታቸው ለባንኩ ላበረከቱት የረጅም ዘመን አገልግሎት ምስጋናቸውን አቅርበው ከምክትል ፕሬዝዳንትነት ኃላፊነታቸው መሰናበታቸውን አረጋግጠዋል።



PUBLISHED ON Dec 30,2025 [ VOL 26 , NO 1340]


[ssba-buttons]

Editorial