FORTUNE+ VIDEO SPONSORED CONTENTS ADVERTORIALS FORTUNE AUDIO Fortune Careers TRADE AFRICA Election 2026 New TIME REMAINING UNTIL ETHIOPIA’S NATIONAL ELECTION 0Days 0Hours 0Minutes 0Seconds


የፈረንሳይ ግዙፍ የገበያ ማዕከል ኢትዮጵያ ሊገባ ነው

የፈረንሳይ ግዙፍ የገበያ ማዕከል ኢትዮጵያ ሊገባ ነው

Jan 9 , 2026.


​በአለም አቀፍ የችርቻሮ ንግድ ዘርፍ ግዙፍ ስም ያለው ካርፎር፣ ከሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ጋር ባደረገው ስምምነት መሰረት የኩዊንስ ሱፐርማርኬትን ተክቶ ስራ ሊጀምር ነው።

​በጀማል አህመድ የሚመራው የሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ፣ በስራ ላይ የሚገኙትን 13 የኩዊንስ ሱፐርማርኬት ቅርንጫፎች በሙሉ ወደ ካርፎር የንግድ ምልክት ለመቀየር ተስማምቷል። የሽግግሩ የመጀመሪያ ምዕራፍ በጎርጎሮሳውያን ዘመን እስከ 2026 አጋማሽ ድረስ እንደሚጠናቀቅ የሚጠበቅ ሲሆን፣ በቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት ውስጥም ተጨማሪ 17 አዳዲስ የካርፎር መደብሮችን ለመክፈት እቅድ ተይዟል።

​ፈረንሳይ ውስጥ በ1950ዎቹ የተመሰረተው ካርፎር፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ የ"ሃይፐር ማርኬት" (Hypermarket) የንግድ ዘይቤን በማስተዋወቅ ፈር ቀዳጅ እንደሆነ ይታወቃል። ኩባንያው በአሁኑ ወቅት በዓለም ዙሪያ ከ40 በላይ ሃገራት ውስጥ የሚገኝ ሲሆን፣ በ30 ሃገራት ውስጥ ከሚገኙ 3,000 የፍራንቻይዝ መደብሮች ጋር በመሆን በአጠቃላይ ወደ 15,000 የሚጠጉ መደብሮች አሉት። በፈረንጆቹ  2024 ዐመተ ምህረት የ94.6 ቢሊዮን ዩሮ የሽያጭ ገቢ ያስመዘገበው ካርፎር፣ በገቢ መጠኑ ከአለማችን ግዙፍ የችርቻሮ ተቋማት ተርታ ይሰለፋል። ኩባንያው በያዝነው ዓመት በ10 አዳዲስ ሃገራት ስራውን ለማስፋፋት እየሰራ ይገኛል።

​በተለይ ትኩስ አትክልትና ፍራፍሬዎችን "ከእርሻ ወደ ገበታ" የአቅርቦት ሰንሰለቱ የሚታወቀው ኩዊንስ ሱፐርማርኬት፣ በዚህ የንግድ ሽርክና መሰረታዊ ለውጦችን ያስተናግዳል ተብሎ ይጠበቃል። በካርፎር ስር የሚደራጁት መደብሮች ከምግብ ነክ ምርቶች በተጨማሪ እንደ የቤት እና የቢሮ ቁሳቁሶች፣ የማብሰያ እቃዎች እና የኤሌክትሮኒክስ ውጤቶችን በማካተት አገልግሎታቸውን እንደሚያሰፉ ይጠበቃል።



PUBLISHED ON Jan 09,2026 [ VOL 26 , NO 1341]


[ssba-buttons]

Editorial