Photo Gallery | 188849 Views | May 06,2019
Dec 24 , 2025.
የፌዴራል ባለሥልጣናት በዲጂታል ፋይናንስ ዘርፍ ላይ በወሰዱት እርምጃ ታግደው የነበሩ የባንክ ሂሳቦችን በከፊል አንስተዋል።
የፍትህ ሚኒስቴር ታኅሣሥ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ባስተላለፈው ትዕዛዝ፣ የያጉት ፔይ (YagoutPay) ዋና ሥራ አስፈጻሚ ተሾመ ዓለማየሁን ጨምሮ የ50 ግለሰቦች የባንክ ሂሳቦች እንዲንቀሳቀሱ አዟል። እነዚህ የባንክ ሂሳቦች ከሦስት ሳምንታት በፊት፣ ህዳር 23 ቀን፣ በዘርፉ የታየ የፋይናንስ ብልሹ አሰራርን ለመመርመር በሚል ታግደው የቆዩ ናቸው።
በተጨማሪም፣ ለዘጠኝ ቀናት የባንክ ሂሳቦቻቸው ተገድበው የነበሩ 10 የዲጂታል ክፍያ (Gateway) ኩባንያዎች እገዳው ተነስቶላቸዋል።
የሚኒስቴሩ የሀብት ማስመለስ መምሪያ ዋና ዳይሬክተር ፀጋ ዋቅጅራ ውሳኔውን ለሁሉም ባንኮች በይፋዊ ደብዳቤ አሳውቀዋል።
እገዳው የተነሳላቸው የክፍያ ተቋማት አሪፍ ፔይ (ArifPay Financial Technologies): አዲስ ፔይ (AddisPay Financial Technologies): ፈናን ፔይ (FenanPay Solutions): ላኪ ፔይ (LakiPay Financial Technologies):
ስታር ፔይ (StarPay Financial Services): ያጉት ፔይ (YagoutPay)
ሳንቲም ፔይ (SantimPay Financial Technologies): ካቻ (Kacha Financial Technology): እና ሲናን ፔይ (Sinan Pay Solutions) ናቸው::
ምንም እንኳን የኩባንያዎቹ የባንክ ሂሳቦች ቢለቀቁም፣ የምርመራው ሂደት ግን ተጠናክሮ ቀጥሏል። የሳንቲም ፔይ፣ የቻፓ ፔይ (Chapa Pay) እና የአሪፍ ፔይ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች አሁንም በፌዴራል ፖሊስ ቁጥጥር ሥር የሚገኙ ሲሆን፣ “ከፍተኛ የፋይናንስ ሕገ-ወጥነት” ተጠርጥረው ምርመራ እየተካሄደባቸው ነው።
ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች እንደጠቆሙት፣ የምርመራው ዋነኛ ትኩረት የግብር ስወራ እና ሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር (Money Laundering) ላይ ነው። የፌዴራል ባለሥልጣናት በፍጥነት እያደገ የመጣውን የዲጂታል ክፍያ ሥርዓት ጥብቅ ቁጥጥር ለማድረግና ሕጋዊ መስመር ለማስያዝ ቅድሚያ ሰጥተው መስራት እንደሚፈልጉ ይናገራሉ።
PUBLISHED ON
Dec 24,2025 [ VOL
26 , NO
1339]
Photo Gallery | 188849 Views | May 06,2019
Photo Gallery | 178681 Views | Apr 26,2019
Photo Gallery | 175285 Views | Oct 06,2021
My Opinion | 141048 Views | Aug 14,2021
May 30 , 2026
Tomorrow, millions of Ethiopians are expected to vote in the seventh national electio...
May 23 , 2026
An International Monetary Fund (IMF) team has spent weeks in Addis Abeba conducting t...
May 16 , 2026
The federal budget tells a troubling story about inflation, debt and reform. The prob...
May 9 , 2026
The Ethiopian state appears to have discovered a fiscal instrument that is politicall...