Photo Gallery | 192943 Views | May 06,2019
Dec 24 , 2025.
የፌዴራል ባለሥልጣናት በዲጂታል ፋይናንስ ዘርፍ ላይ በወሰዱት እርምጃ ታግደው የነበሩ የባንክ ሂሳቦችን በከፊል አንስተዋል።
የፍትህ ሚኒስቴር ታኅሣሥ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ባስተላለፈው ትዕዛዝ፣ የያጉት ፔይ (YagoutPay) ዋና ሥራ አስፈጻሚ ተሾመ ዓለማየሁን ጨምሮ የ50 ግለሰቦች የባንክ ሂሳቦች እንዲንቀሳቀሱ አዟል። እነዚህ የባንክ ሂሳቦች ከሦስት ሳምንታት በፊት፣ ህዳር 23 ቀን፣ በዘርፉ የታየ የፋይናንስ ብልሹ አሰራርን ለመመርመር በሚል ታግደው የቆዩ ናቸው።
በተጨማሪም፣ ለዘጠኝ ቀናት የባንክ ሂሳቦቻቸው ተገድበው የነበሩ 10 የዲጂታል ክፍያ (Gateway) ኩባንያዎች እገዳው ተነስቶላቸዋል።
የሚኒስቴሩ የሀብት ማስመለስ መምሪያ ዋና ዳይሬክተር ፀጋ ዋቅጅራ ውሳኔውን ለሁሉም ባንኮች በይፋዊ ደብዳቤ አሳውቀዋል።
እገዳው የተነሳላቸው የክፍያ ተቋማት አሪፍ ፔይ (ArifPay Financial Technologies): አዲስ ፔይ (AddisPay Financial Technologies): ፈናን ፔይ (FenanPay Solutions): ላኪ ፔይ (LakiPay Financial Technologies):
ስታር ፔይ (StarPay Financial Services): ያጉት ፔይ (YagoutPay)
ሳንቲም ፔይ (SantimPay Financial Technologies): ካቻ (Kacha Financial Technology): እና ሲናን ፔይ (Sinan Pay Solutions) ናቸው::
ምንም እንኳን የኩባንያዎቹ የባንክ ሂሳቦች ቢለቀቁም፣ የምርመራው ሂደት ግን ተጠናክሮ ቀጥሏል። የሳንቲም ፔይ፣ የቻፓ ፔይ (Chapa Pay) እና የአሪፍ ፔይ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች አሁንም በፌዴራል ፖሊስ ቁጥጥር ሥር የሚገኙ ሲሆን፣ “ከፍተኛ የፋይናንስ ሕገ-ወጥነት” ተጠርጥረው ምርመራ እየተካሄደባቸው ነው።
ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች እንደጠቆሙት፣ የምርመራው ዋነኛ ትኩረት የግብር ስወራ እና ሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር (Money Laundering) ላይ ነው። የፌዴራል ባለሥልጣናት በፍጥነት እያደገ የመጣውን የዲጂታል ክፍያ ሥርዓት ጥብቅ ቁጥጥር ለማድረግና ሕጋዊ መስመር ለማስያዝ ቅድሚያ ሰጥተው መስራት እንደሚፈልጉ ይናገራሉ።
PUBLISHED ON
Dec 24,2025 [ VOL
26 , NO
1339]
Photo Gallery | 192943 Views | May 06,2019
Photo Gallery | 182841 Views | Apr 26,2019
Photo Gallery | 179611 Views | Oct 06,2021
My Opinion | 145094 Views | Aug 14,2021
Aug 8 , 2026
The World Bank asks readers to picture a mother in rural Ethiopia who has never held...
Jul 31 , 2026
Weldu Yiheysh has not read the Pacific temperature charts. He does not need to. In Shibta District of Enderta Wereda, in...
Jul 25 , 2026
Ideally, citizens who have paid income tax all year should not have to reach for thei...
Jul 18 , 2026
Pressed in Parliament on jobs and household incomes, Prime Minister Abiy Ahmed (PhD)...