Photo Gallery | 189860 Views | May 06,2019
Jan 12 , 2026.
መንግሥታዊው የፖሊሲ ባንክ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ (ኢልባ) በአመራር እርከኑ ላይ አምስት አዳዲስ ምክትል ፕሬዝዳንቶችን ዛሬ ጥር 4 ቀን 2018 ዓ.ም. አግኝቷል።
የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ ብሩክ ታየ (ዶ/ር) በባንኩ ውስጥ ረጅም ዘመን ያገለገሉትን ጌታቸው ዋቄን በመተካት የኔነህ ግዛውን የኮርፖሬት አገልግሎት ዘርፍ ምክትል ፕሬዝዳንት አድርገው ሾመዋል። በተመሳሳይ ጌታሰው ፈንታው የአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ፋይናንስ ዘርፍን በምክትል ፕሬዝዳንትነት እንዲመሩ ተመድበዋል።
አቶ ጌታቸው በላይ የኮርፖሬት ደንበኞች አስተዳደር ምክትል ፕሬዝዳንት፤ አበባው ሲራጅ የፋይናንስና ዓለም አቀፍ ባንክ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት፤ እና ደሳለኝ ኃይሌ የኢንፎርሜሽን ሲስተምና ዲጂታል ባንክ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነዋል።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ የሆኑት ብሩክ፣ የቀድሞውን የብሔራዊ ባንክ ገዢ አቶ ተክለወልድ አጥናፉን ተክተው የልማት ባንክ የቦርድ ሰብሳቢ ከሆኑ ወዲህ በባንኩ የአመራር መዋቅር ላይ ፈጣን ለውጦች እየታዩ ነው። ሰሞኑን እመቤት መለሰን (ዶ/ር) በመተካት የባንኩ ፕሬዝዳንት ሆነው የተሾሙት ኢሳያስ ካሳ (ዶ/ር)፣ ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን መሥራች አመራርነት በብሩክ ሥር ሲሠሩ የቆዩ መሆኑ ይታወሳል።
ፎርቹን የተመለከተው የቦርድ ሰብሳቢው የሹመት ደብዳቤና መግለጫ እንደሚያሳየው፣ አዲሶቹ ተሿሚዎች የተጣለባቸውን ኃላፊነት በሙሉ ቁርጠኝነት እንዲወጡ ጥሪ ቀርቦላቸዋል።
PUBLISHED ON
Jan 12,2026 [ VOL
26 , NO
1342]
Photo Gallery | 189860 Views | May 06,2019
Photo Gallery | 179585 Views | Apr 26,2019
Photo Gallery | 176218 Views | Oct 06,2021
My Opinion | 141917 Views | Aug 14,2021
Jun 13 , 2026
The recent policy decision to fully open freight forwarding to foreign capital may be...
Jun 6 , 2026
For a political veteran as controversial as Getachew Reda, last week's national elect...
May 30 , 2026
Tomorrow, millions of Ethiopians are expected to vote in the seventh national electio...
May 23 , 2026
An International Monetary Fund (IMF) team has spent weeks in Addis Abeba conducting t...