Photo Gallery | 192200 Views | May 06,2019
Jan 12 , 2026.
መንግሥታዊው የፖሊሲ ባንክ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ (ኢልባ) በአመራር እርከኑ ላይ አምስት አዳዲስ ምክትል ፕሬዝዳንቶችን ዛሬ ጥር 4 ቀን 2018 ዓ.ም. አግኝቷል።
የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ ብሩክ ታየ (ዶ/ር) በባንኩ ውስጥ ረጅም ዘመን ያገለገሉትን ጌታቸው ዋቄን በመተካት የኔነህ ግዛውን የኮርፖሬት አገልግሎት ዘርፍ ምክትል ፕሬዝዳንት አድርገው ሾመዋል። በተመሳሳይ ጌታሰው ፈንታው የአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ፋይናንስ ዘርፍን በምክትል ፕሬዝዳንትነት እንዲመሩ ተመድበዋል።
አቶ ጌታቸው በላይ የኮርፖሬት ደንበኞች አስተዳደር ምክትል ፕሬዝዳንት፤ አበባው ሲራጅ የፋይናንስና ዓለም አቀፍ ባንክ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት፤ እና ደሳለኝ ኃይሌ የኢንፎርሜሽን ሲስተምና ዲጂታል ባንክ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነዋል።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ የሆኑት ብሩክ፣ የቀድሞውን የብሔራዊ ባንክ ገዢ አቶ ተክለወልድ አጥናፉን ተክተው የልማት ባንክ የቦርድ ሰብሳቢ ከሆኑ ወዲህ በባንኩ የአመራር መዋቅር ላይ ፈጣን ለውጦች እየታዩ ነው። ሰሞኑን እመቤት መለሰን (ዶ/ር) በመተካት የባንኩ ፕሬዝዳንት ሆነው የተሾሙት ኢሳያስ ካሳ (ዶ/ር)፣ ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን መሥራች አመራርነት በብሩክ ሥር ሲሠሩ የቆዩ መሆኑ ይታወሳል።
ፎርቹን የተመለከተው የቦርድ ሰብሳቢው የሹመት ደብዳቤና መግለጫ እንደሚያሳየው፣ አዲሶቹ ተሿሚዎች የተጣለባቸውን ኃላፊነት በሙሉ ቁርጠኝነት እንዲወጡ ጥሪ ቀርቦላቸዋል።
PUBLISHED ON
Jan 12,2026 [ VOL
26 , NO
1342]
Photo Gallery | 192200 Views | May 06,2019
Photo Gallery | 181972 Views | Apr 26,2019
Photo Gallery | 178710 Views | Oct 06,2021
My Opinion | 144229 Views | Aug 14,2021
Jul 25 , 2026
Ideally, citizens who have paid income tax all year should not have to reach for thei...
Jul 18 , 2026
Pressed in Parliament on jobs and household incomes, Prime Minister Abiy Ahmed (PhD)...
Jul 11 , 2026
At a market stall, reform arrives without a communique. It comes as a higher transpor...
Jul 4 , 2026
In the goldfields of the Benishangul-Gumuz Regional State, Ethiopia's balance-of-paym...