Photo Gallery | 185861 Views | May 06,2019
Feb 4 , 2026.
ጸደይ ባንክ የምጣኔ ሀብት ባለሙያና የቀድሞውን የብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥ ዮሐንስ አያሌውን (ዶ/ር) በፕሬዝዳንትነት ለመሰየም ተዘጋጅቷል።
በአማራ ክልል ከነበረው የብድርና ቁጠባ ተቋምነት ወደ ባንክ ካደገ በኋላ ሁለተኛው ፕሬዝዳንት ሊሆን የሚችለውን ዕጩ ለይቷል። ይህ የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ውሳኔ ባንኩ በባለፈው ሒሳብ ዓመት የ2.13 ቢሊዮን ብር ኪሳራ ባጋጠመው ወሳኝ ወቅት ላይ የቀረበ ነው።
ዮሐንስ በብሔራዊ ባንክ ተቀባይነት ካገኙ ባለፈው ጥር ወር ላይ ስልጣን የለቀቁትን የጸዳይ ባንክ መስራች ፕሬዝዳንት መኮንን የለውምወሰንን የሚተኩ ሲሆን፤ ካለፈው ጥር ወር ጀምሮ የሺእመቤት ተፈራ ባንኩን በጊዜያዊነት በመምራት ላይ ይገኛሉ።
ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ የሥራ ልምድ ያላቸው ዮሐንስ፣ የቀድሞ የሙያ ዘመናቸው ለዘጠኝ ዓመታት በብሔራዊ ባንክ ዋና የምጣኔ ሀብት ባለሙያነት የተቃኘ ነበር። በፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት እንዲሁም በአፍሪካ ንግድና ኢንቨስትመንት ልማት ኢንሹራንስ የሀገር ውስጥ ዳይሬክተር በመሆንም አገልግለዋል። በተለይም እ.ጎ.አ ከ2018 እስከ 2022 ዓ.ም. በኢትዮጵያ ልማት ባንክ በቆዩባቸው ዓመታት ተቋሙን ከተከማቸ የማይመለስ ብድር በማላቀቅ ወደ ንግድ ተኮር የብድር አሰጣጥ ለማሸጋገር ያደረጉት ጥረት ውጤት የታየበት እንደነበር ይታወሳል። ዮሐንስ በቅርቡ የአማራ ባንክ ፕሬዝዳንት ሆነው በሰሩባቸው 16 ወራት ባንኩ በገንዘብ እጥረትና በውስጥ ቀውስ ውስጥ በነበረበት ወቅት ተረክበውት፣ ከኪሳራ በማውጣት 655 ሚሊዮን ብር ከታክስ በፊት ትርፍ እንዲያስመዘግብና የ85 በመቶ ዕድገት እንዲያሳይ ማስቻላቸው ይታወሳል።
PUBLISHED ON
Feb 04,2026 [ VOL
26 , NO
1345]
Photo Gallery | 185861 Views | May 06,2019
Photo Gallery | 175902 Views | Apr 26,2019
Photo Gallery | 171462 Views | Oct 06,2021
My Opinion | 139414 Views | Aug 14,2021
May 9 , 2026
The Ethiopian state appears to have discovered a fiscal instrument that is politicall...
May 2 , 2026
By the time Ethiopia's National Dialogue Commission (ENDC) reached the end of its fir...
Apr 25 , 2026
In a political community, official speeches show what governments want their citizens...
For much of the past three decades, Ethiopia occupied a familiar place in the Western...