Photo Gallery | 185863 Views | May 06,2019
Jan 21 , 2026.
ዋቢ ሸበሌ ሆቴል ወደ ሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ መዘዋወሩን ተከትሎ አዲስ ምዕራፍ ጀምሯል። በኢትዮጵያ የንግድና የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ውስጥ ትልቅ ስፍራ የሚሰጠው ይህ የባለቤትነት ሽግግር የሆቴሉን ረጅም ጉዞ ተከትሎ የተመዘገበ አዲስ ክንውን ሆኖ ተመዝግቧል።
ሆቴሉ በ1950ዎቹ መገባደጃ ላይ በንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ አማካኝነት ለልጅ ልጆቻቸው ገቢ እንዲያስገኝ ታስቦ የተገነባ ቢሆንም፣ በደርግ ዘመን በመንግሥት ከተወረሰ በኋላ በ2000ዎቹ መጀመሪያ ላይ ግን ለንጉሣዊ ቤተሰቡ ወራሾች ተመልሷል።
ይህንን ታሪካዊ የንብረት ዝውውር በዛሬው ዕለት ጥር 13 ቀን 2018 ዓ.ም. ያከናወኑት በሜድሮክ በኩል ዋና ሥራ አስፈፃሚው ጀማል አህመድ እና በሆቴሉ በኩል የቦርድ ፀሐፊው በሆኑት በዕደማርያም መኮንን ኃይለሥላሴ (ልዑል) መካከል በተደረገ የስምምነት ፊርማ ነው።
በዕደማርያም በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ሚድሮክ ለታሪክና ለዘመናዊነት ያለውን ራዕይ ያደነቁ ሲሆን፣ ድርጅቱ የሆቴሉን ጥንታዊ ገፅታ ሳይለቅ ዘመናዊ መልክ እንዲይዝ ለማድረግ የገባውን ቃልም አረጋግጠዋል። በ40 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈው ይህ ሆቴል፣ በሚድሮክ ሥር ከገባ በኋላ በማርዮት ኢንተርናሽናል የ"Autograph Collection" መስፈርት መሠረት ከፍተኛ እድሳት ተደርጎለት ዳግም እንደከፈት ታውቋል። ይህም ሚድሮክ ሆቴሉን ዓለም አቀፍ ደንበኞችን ለማስተናገድ በሚያስችል ከፍተኛ ደረጃ ለማድረስ ያለውን ፍላጎት ያሳያል ተብሏል።
ግዥው የተፈፀመው ኢትዮጵያ 32ኛውን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን (COP32) ለማስተናገድ እየተዘጋጀች ባለችበት ወቅት ነው::
PUBLISHED ON
Jan 21,2026 [ VOL
26 , NO
1343]
Photo Gallery | 185863 Views | May 06,2019
Photo Gallery | 175904 Views | Apr 26,2019
Photo Gallery | 171466 Views | Oct 06,2021
My Opinion | 139414 Views | Aug 14,2021
May 9 , 2026
The Ethiopian state appears to have discovered a fiscal instrument that is politicall...
May 2 , 2026
By the time Ethiopia's National Dialogue Commission (ENDC) reached the end of its fir...
Apr 25 , 2026
In a political community, official speeches show what governments want their citizens...
For much of the past three decades, Ethiopia occupied a familiar place in the Western...