FORTUNE+ VIDEO SPONSORED CONTENTS ADVERTORIALS FORTUNE AUDIO Fortune Careers TRADE AFRICA Election 2026 New TIME REMAINING UNTIL ETHIOPIA’S NATIONAL ELECTION 0Days 0Hours 0Minutes 0Seconds



ኢግል ላየን ሲስተም ቴክኖሎጂ ግሩፕ እና ፀደይ ባንክ በሀገራችን የግብርና ግብዓት ሥርጭትን በዲጂታል ቴክኖሎጂ በማዘመን ቀልጣፋና ግልጽ ለማድረግ የሚያስችል ታሪካዊ የስምምነት ሰነድ በትናንትናው ዕለት በፀደይ ባንክ ዋና መሥሪያ ቤት  ተፈራርመዋል ፡፡

በዚህ ትብብር መሠረት የኢግል ላየን ሲስተም ቴክኖሎጂ ግሩፕ የፈጠራ ውጤት የሆነው "Get Fee" የተሰኘው ዲጂታል ሲስተም ሥራ ላይ የሚውል ሲሆን፣ አሠራሩ ከኤጀንሲዎች እስከ አርሶአደሮች ድረስ ያለውን የግብርና ግብዓት ሥርጭት ሂደት በጥራትና በስፋት ለማከናወን ያስችላል፡፡


የኢግል ላየን ሲስተም ቴክኖሎጂ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ በእርሱፈቃድ ጌታቸው እንደገለጹት፣ ድርጅታቸው በፋይናንስ ቴክኖሎጂ ዘርፍ ከ26 በላይ ምርቶችን በማበልፅግ ለገበያ ያቀረበና አሁንም ቴክኒዎሎጂን በማቅረብ ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል Get Fee  በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ  አርሶ አደሮች እየተጠቀሙበት የሚገኝ የግብዓት ማሠራጫ ሲስተም ነው፡፡

ሲስተሙ ከፍተኛ ገንዘብ በሥርዓት እንዲንቀሳቀስ የሚያስችል ትልቅ አቅም ያለው መሆኑንና በጥሬ ገንዘብ በሚደረጉ ግብይቶች ምክንያት የሚከሰቱ የሀብት ምዝበራዎችንና ተያያዥ ስጋቶችን ሙሉ በሙሉ በማስቀረት ዘመናዊና ግልጽ አሠራርን ለመተግበር የሚያስችል መሆኑን አቶ በእርሱፈቃድ አብራርተዋል፡፡



አክለውም፣ ለግብርናው ዘርፍ መዘመንና ለምርት እድገት ላለፉት 30 ዓመታት በገጠሩ ማኅበረሰብ ውስጥ ሰፊ መሠረት ጥሎ ሲሠራ ከቆየው አንጋፋው ፀደይ ባንክ ጋር የመሥራት ዕድል በማግኘታቸው ደስታቸውን ገልጸው፣ ስምምነቱን በአጭር ቀናት ውስጥ ወደ ሙሉ ተግባር ለማስገባት ድርጅታቸው ሙሉ ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡

በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የፀደይ ባንክ ፕሬዝዳንት ዶክተር ዮሐንስ አያሌው በበኩላቸው፣ ይህ ትብብር ባንኩ እያከናወናቸው ከሚገኙ ታላላቅ የማሻሻያ ሥራዎች መካከል ትልቁን ቦታ የሚይዝ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አሠራሩ የግብዓት ሥርጭትን በማዘመን ከአርሦ አደሮች ጀምሮ የበርካታ የማኅበረሰብ ክፍሎችንና የተቋማትን መሠረታዊ ችግር እንደሚፈታ የጠቆሙት ዶክተር ዮሐንስ፣ እያንዳንዱ ክፍያ ግልጽነት ባለው መንገድ እንዲያልፍ በማድረግ የሀገር ሀብት በጥቅም ላይ እንዲውል የማድረጉ ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑን አብራርተዋል፡፡


Eaglelion system technology Group,

Ethiopian Company!



PUBLISHED ON Aug 26,2026 [ VOL 27 , NO 1374]


[ratemypost]



[ssba-buttons]

Put your comments here

N.B: A submit button will appear once you fill out all the required fields.


Editors' Pick



Editorial