Photo Gallery | 185859 Views | May 06,2019
Jan 12 , 2026.
መንግሥታዊው የፖሊሲ ባንክ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ (ኢልባ) በአመራር እርከኑ ላይ አምስት አዳዲስ ምክትል ፕሬዝዳንቶችን ዛሬ ጥር 4 ቀን 2018 ዓ.ም. አግኝቷል።
የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ ብሩክ ታየ (ዶ/ር) በባንኩ ውስጥ ረጅም ዘመን ያገለገሉትን ጌታቸው ዋቄን በመተካት የኔነህ ግዛውን የኮርፖሬት አገልግሎት ዘርፍ ምክትል ፕሬዝዳንት አድርገው ሾመዋል። በተመሳሳይ ጌታሰው ፈንታው የአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ፋይናንስ ዘርፍን በምክትል ፕሬዝዳንትነት እንዲመሩ ተመድበዋል።
አቶ ጌታቸው በላይ የኮርፖሬት ደንበኞች አስተዳደር ምክትል ፕሬዝዳንት፤ አበባው ሲራጅ የፋይናንስና ዓለም አቀፍ ባንክ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት፤ እና ደሳለኝ ኃይሌ የኢንፎርሜሽን ሲስተምና ዲጂታል ባንክ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነዋል።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ የሆኑት ብሩክ፣ የቀድሞውን የብሔራዊ ባንክ ገዢ አቶ ተክለወልድ አጥናፉን ተክተው የልማት ባንክ የቦርድ ሰብሳቢ ከሆኑ ወዲህ በባንኩ የአመራር መዋቅር ላይ ፈጣን ለውጦች እየታዩ ነው። ሰሞኑን እመቤት መለሰን (ዶ/ር) በመተካት የባንኩ ፕሬዝዳንት ሆነው የተሾሙት ኢሳያስ ካሳ (ዶ/ር)፣ ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን መሥራች አመራርነት በብሩክ ሥር ሲሠሩ የቆዩ መሆኑ ይታወሳል።
ፎርቹን የተመለከተው የቦርድ ሰብሳቢው የሹመት ደብዳቤና መግለጫ እንደሚያሳየው፣ አዲሶቹ ተሿሚዎች የተጣለባቸውን ኃላፊነት በሙሉ ቁርጠኝነት እንዲወጡ ጥሪ ቀርቦላቸዋል።
PUBLISHED ON
Jan 12,2026 [ VOL
26 , NO
1342]
Photo Gallery | 185859 Views | May 06,2019
Photo Gallery | 175900 Views | Apr 26,2019
Photo Gallery | 171458 Views | Oct 06,2021
My Opinion | 139414 Views | Aug 14,2021
May 9 , 2026
The Ethiopian state appears to have discovered a fiscal instrument that is politicall...
May 2 , 2026
By the time Ethiopia's National Dialogue Commission (ENDC) reached the end of its fir...
Apr 25 , 2026
In a political community, official speeches show what governments want their citizens...
For much of the past three decades, Ethiopia occupied a familiar place in the Western...