መጋቢት 12/ 2014 አዲስ አበባ፣
ኢትዮጵያ፡ በአውሮፓ ህብረት እገዛ በኢትዮጵያ የንግድ ስራ አመቺነትን ለ ማ ሳ ለ ጥ እ የ ተ ተ ገ በ ረ ባ ለ ው ፕሮጀክት ስር የተከናወነ ጥናትን የተመለከተ ወርክሾፕ መጋቢት 12 ቀን 2014 ዓም ተካሄደ፡፡ ፡፡ ወርክሾፑ በኢትዮጵያ የገቢዎች ሚኒስቴር መስርያ ቤት ውስጥ ከፕሮጀክቱ በተገኘ ድጋፍ በኔትዎርከ ፤ ዳታ
ሴንተር እና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ደህንነት መሰረተ ልማት ላይ የተደረገ ፍተሻና የተሻሻለ የኔትዎርክ ዲዛይንን ባካተተ ዶክመንት ላይ ሲሆን የገቢዎች ሚኒስቴር ተወካዮች እና በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት ልኡካን ተወካዮች የተገኙበት ነበር፡፡
የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ኔትዎርክ ማሻሻያ ስራው የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት የንግድ ስራ አመቺነትን ለማሳለጥ ያወጣውን የዲጂታላይዜሽን ሪፎርም ለመተግበር በገቢዎች ሚኒስትር ታቅዶ፣ በዚህ ፕሮጀክት ድጋፍ የተሰራ ነው፡፡ የፕሮጀክቱ አጠቃላይ ዓላማ በኢትዮጵያ ያለውን የንግድ ሁኔታ ማሻሻል፣ የግሉን ዘርፍ
ልማት ማበረታታት እንዲሁም የንግድ ስራ አመቺነትን በማሳለጥ የስራ እና የገቢ እድሎችን መፍጠር ነው፡፡
ፕሮጀክቱ ከየካቲት 2013 ጀምሮ እስከ 2016 ድረስ ለሶስት አመታት ያህል የሚቆይ ሲሆን፣ በዚህ ፕሮጀክት ማዕቀፍ ውስጥ ድጋፍ የሚያገኙ ተቋሞች የገቢዎች ሚኒስቴር፣ የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ፣ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ እንዲሁም በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት ቢዝነስ
ፎረም ናቸው፡፡
ከገቢዎች ሚኒስቴር ጋር በተያያዘ ፕሮጀክቱ የቴክኒካል እና በተለያዩ ዘርፎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ይሰጣል፡ ፡ ይህም ድጋፍ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመን ምክረ ሀሳቦችን፣ ሞያዊ ድጋፍን እና ስልጠናዎችን አካቶ ይዟል፡፡በተጨማሪ በገቢዎች ሚኒስቴር ያለውን የግብር አሰባሰብ ስርዓት ቴክኒካል አቅም የማጎልበት እንዲሁም የመስርያ ቤቱን የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ኔትዎርክ የማሻሻል እገዛ ያደርጋል፡፡
በወርክሾፑ የተገኙት የአውሮፓ ህብረት ልዑካን ቡድን ተወካይ በመክፈቻ ንግግራቸው በኢትዮጵያ መንግስት የግል ሴክተሩ በኢኮኖሚው የሚጫወተውን ሚና ለማሳደግ በተለይም የንግድና ኢንቨስትመንት ከባቢውን ምቹ እና ተወዳዳሪ እንዲሆን እየተሰራ ያለውን የሪፎርም ስራ በማድነቅ የአውሮፓ ህብረት እያደረገ ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል፡፡
የ ገ ቢ ዎ ች ሚ ኒ ስ ቴ ር ተ ወ ካ ይ በበኩላቸው በፕሮጀክቱ የተከናወነው የኔትዎርክ ማሻሻል ስራ የጠቅላይ ሚኒስቴር ፅህፈት ቤት እየመራው ካለው የንግድ ስራ አመቺነትን የማሳለጥ ፕሮግራም ጋር በተያያዘ እየተሰራ ላለው የዲጂታላይዜሽን ለ ው ጥ ክ ፍ ተ ኛ አ ስ ተ ዋ ፅ ዖ እንደሚያበረክት ገልፀዋል፡፡
የኢትዮጵያን የንግድና ኢንቨስትመንት ከባቢ ምቹ፣ ተወዳዳሪና ተመራጭ ለማድረግ እንዲሁም የዓለም ባንክ የ’Doing Business’ ደረጃዋን ማሻሻል እንዲቻል መንግስት ከፍተኛ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ በዚህም መሰረት ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ምቹ ሃገራት ደረጃዋን እ.ኤ.አ በ2019 ከነበረችበት 159 ከፍ በማድረግ ከቀዳሚዎቹ መቶ አገራት ተርታ እንድትሰለፍ ለማስቻል ታህሳስ 17 ቀን 2011 ዓ.ም. ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የሚመሩት ብሔራዊ ኮሚቴ ተመስርቶ ወደ ስራ መግባቱ የሚታወስ ነው።
PUBLISHED ON
Mar 28,2022 [ VOL
22 , NO
1144]
Dec 24 , 2022
Biniam Mikru heads the department of cabinet affairs under Mayor Adanech Abiebie. But...
Jul 2 , 2022 . By RUTH TAYE
On a rainy afternoon last week, a coffee processing facility in the capital's Akaki-Qality District was abuzz with activ...
Nov 27 , 2021
Against my will, I have witnessed the most terrible defeat of reason and the most sa...
Nov 13 , 2021
Plans and reality do not always gel. They rarely do in a fast-moving world. Every act...
Mar 25 , 2023
At a crossroads, Addis Abeba finds itself on the precipice of monumental transformati...
Mar 18 , 2023
Ethiopia's economy once hailed as a paragon of growth and development, now faces a co...
Mar 11 , 2023
Ethiopia is rapidly emerging as one of China's top African debtors, second only to An...
Mar 4 , 2023
Once again, Ethiopia has claimed international attention in the past few weeks for re...