መጋቢት 12/ 2014 አዲስ አበባ፣
ኢትዮጵያ፡ በአውሮፓ ህብረት እገዛ በኢትዮጵያ የንግድ ስራ አመቺነትን ለ ማ ሳ ለ ጥ እ የ ተ ተ ገ በ ረ ባ ለ ው ፕሮጀክት ስር የተከናወነ ጥናትን የተመለከተ ወርክሾፕ መጋቢት 12 ቀን 2014 ዓም ተካሄደ፡፡ ፡፡ ወርክሾፑ በኢትዮጵያ የገቢዎች ሚኒስቴር መስርያ ቤት ውስጥ ከፕሮጀክቱ በተገኘ ድጋፍ በኔትዎርከ ፤ ዳታ
ሴንተር እና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ደህንነት መሰረተ ልማት ላይ የተደረገ ፍተሻና የተሻሻለ የኔትዎርክ ዲዛይንን ባካተተ ዶክመንት ላይ ሲሆን የገቢዎች ሚኒስቴር ተወካዮች እና በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት ልኡካን ተወካዮች የተገኙበት ነበር፡፡
የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ኔትዎርክ ማሻሻያ ስራው የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት የንግድ ስራ አመቺነትን ለማሳለጥ ያወጣውን የዲጂታላይዜሽን ሪፎርም ለመተግበር በገቢዎች ሚኒስትር ታቅዶ፣ በዚህ ፕሮጀክት ድጋፍ የተሰራ ነው፡፡ የፕሮጀክቱ አጠቃላይ ዓላማ በኢትዮጵያ ያለውን የንግድ ሁኔታ ማሻሻል፣ የግሉን ዘርፍ
ልማት ማበረታታት እንዲሁም የንግድ ስራ አመቺነትን በማሳለጥ የስራ እና የገቢ እድሎችን መፍጠር ነው፡፡
ፕሮጀክቱ ከየካቲት 2013 ጀምሮ እስከ 2016 ድረስ ለሶስት አመታት ያህል የሚቆይ ሲሆን፣ በዚህ ፕሮጀክት ማዕቀፍ ውስጥ ድጋፍ የሚያገኙ ተቋሞች የገቢዎች ሚኒስቴር፣ የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ፣ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ እንዲሁም በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት ቢዝነስ
ፎረም ናቸው፡፡
ከገቢዎች ሚኒስቴር ጋር በተያያዘ ፕሮጀክቱ የቴክኒካል እና በተለያዩ ዘርፎች የአቅም ግንባታ ድጋፍ ይሰጣል፡ ፡ ይህም ድጋፍ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመን ምክረ ሀሳቦችን፣ ሞያዊ ድጋፍን እና ስልጠናዎችን አካቶ ይዟል፡፡በተጨማሪ በገቢዎች ሚኒስቴር ያለውን የግብር አሰባሰብ ስርዓት ቴክኒካል አቅም የማጎልበት እንዲሁም የመስርያ ቤቱን የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ኔትዎርክ የማሻሻል እገዛ ያደርጋል፡፡
በወርክሾፑ የተገኙት የአውሮፓ ህብረት ልዑካን ቡድን ተወካይ በመክፈቻ ንግግራቸው በኢትዮጵያ መንግስት የግል ሴክተሩ በኢኮኖሚው የሚጫወተውን ሚና ለማሳደግ በተለይም የንግድና ኢንቨስትመንት ከባቢውን ምቹ እና ተወዳዳሪ እንዲሆን እየተሰራ ያለውን የሪፎርም ስራ በማድነቅ የአውሮፓ ህብረት እያደረገ ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል፡፡
የ ገ ቢ ዎ ች ሚ ኒ ስ ቴ ር ተ ወ ካ ይ በበኩላቸው በፕሮጀክቱ የተከናወነው የኔትዎርክ ማሻሻል ስራ የጠቅላይ ሚኒስቴር ፅህፈት ቤት እየመራው ካለው የንግድ ስራ አመቺነትን የማሳለጥ ፕሮግራም ጋር በተያያዘ እየተሰራ ላለው የዲጂታላይዜሽን ለ ው ጥ ክ ፍ ተ ኛ አ ስ ተ ዋ ፅ ዖ እንደሚያበረክት ገልፀዋል፡፡
የኢትዮጵያን የንግድና ኢንቨስትመንት ከባቢ ምቹ፣ ተወዳዳሪና ተመራጭ ለማድረግ እንዲሁም የዓለም ባንክ የ’Doing Business’ ደረጃዋን ማሻሻል እንዲቻል መንግስት ከፍተኛ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ በዚህም መሰረት ኢትዮጵያ በንግድና ኢንቨስትመንት ምቹ ሃገራት ደረጃዋን እ.ኤ.አ በ2019 ከነበረችበት 159 ከፍ በማድረግ ከቀዳሚዎቹ መቶ አገራት ተርታ እንድትሰለፍ ለማስቻል ታህሳስ 17 ቀን 2011 ዓ.ም. ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የሚመሩት ብሔራዊ ኮሚቴ ተመስርቶ ወደ ስራ መግባቱ የሚታወስ ነው።
PUBLISHED ON
Mar 28,2022 [ VOL
22 , NO
1144]
Jul 13 , 2024 . By AKSAH ITALO
Investors who rely on tractors, trucks, and field vehicles for commuting, transportin...
Jul 13 , 2024 . By MUNIR SHEMSU
The cracks in Ethiopia's higher education system were laid bare during a synthesis re...
Jul 13 , 2024 . By AKSAH ITALO
Construction authorities have unveiled a price adjustment implementation manual for s...
Jul 13 , 2024
The banking industry is experiencing a transformative period under the oversight of N...
Jul 20 , 2024
In a volatile economic environment, sudden policy reversals leave businesses reeling...
Jul 13 , 2024
Policymakers are walking a tightrope, struggling to generate growth and create millio...
Jul 7 , 2024
The federal budget has crossed a symbolic threshold, approaching the one trillion Bir...
Jun 29 , 2024
In a spirited bid for autonomy, the National Bank of Ethiopia (NBE), under its younge...